Wednesday, June 25, 2014
Saturday, June 21, 2014
እድለቢስቷ
ለስለስ ያለ ንፋስ
ሽው ሽው ሽውሽውሽው፣
አዋጅ መዓዛዋን ሲያዋህደው፣
መዓዛዋ ገማና፣
ውበቷ ቆሸሸና፣
ምኞቷ መከነና፣
ቅረች መና፣
ያልተመረቀላት ፍካቷ፣
እድለቢስቷ!
==================
ሽው ሽው ሽውሽውሽው፣
አዋጅ መዓዛዋን ሲያዋህደው፣
የንብ መንጋ
ዠበብ ዠበብ
ዠበበብ ፣
እርፍ ቅስም
ቅስም ቅስም ቅስምስምስም፣
እርፍ ቅስም
ቅስም ቅስም ቅስምስምስም፣
ማር ስርት የሚጥም፣
ውብ ቢራቢሮዎች
ብርር ብርር ብርርር፣
ማራኪ ህብር ፍጥር፣
ሲያደርጉ ማየት ነበረ ምኞቷ፣
ያልፈካችው ለጋ እምቡጢቷ፣
ግና ግና
በለስላሳው ፋንታ አውሎ ንፋስ፣
ንቦቹን በዝንብ ጭርንቁስቁስ፣
ቢራቢሮዎቹን በትንኝ ግብስብስ፣
ተፈጥሮ ተካችና፣
የምቡጢቷ፣ መዓዛዋ ገማና፣
ውበቷ ቆሸሸና፣
ምኞቷ መከነና፣
ቅረች መና፣
ያልተመረቀላት ፍካቷ፣
እድለቢስቷ!
==================
©እኔ ነኝ
Saturday, May 31, 2014
የኋልዮሽ ጉዞ
መጋቢት ወር
ነው። የፋክት መፅሔትን ቅፅ
2 ቁጥር 37 እያነበብኩ።
ፕሮፌሰሩ (ፕ/ር
መስፍን ወ/ማሪያም) “መጠላለፍ ወደየት እየመራን ነው?” በሚል መጠይቅ የፃፉት ፅሁፍ እንደኔ የሃይማኖንቶችን መቻቻል፣ መፈቃቀር፣ መረዳዳትና መከባበርን ልምዱ
አድርጎ ላደገ ኢትዮጵያዊ ያስደነግጣል፤ ያስፈራል። ፕሮፌሰሩ በፅሁፋቸው ካነሷቸው ሃሳቦች ካንዱ በስተቀር ሌሎቹን የተለያየ ቦታ ስላነበብኳችው ቢያስፈሩኝም አዲሴ አልነበሩም። እንደሚከተለው የገለፁት ግን
ለኔ አዲሴና በጣምም ውስጤን የነካኝ ነበር።
“… አሁን ደግሞ ሌላ ማዘዣ ሰማሁ፤ የስ የሚለው የውሃ ጠርሙስ ላይ እንስራ የተሸከመችው ኮረዳ መስቀል አድርጋ ነበር፤ ልጅቱ ከነ መስቀሏ የምትታይበትን ውሃ እስላሞች አንገዛም ስላሉ ነጋዴዎች መስቀሉን አወለቁባት! ይህንን ማዘዣ ላወጣው አክራሪ እስላም ወረባቦ ቅዳሜ ገበያ ሄዶ እንዲጎበኝ አሳስበዋለው፤ ዛሬ ተለውጦ እንደሆነ አላውቅም እንጂ እኔ ብዙ ግዜ ተመላልሼ እንዳየሁት የወረባቦ ኮረዶች ሁሉ ትልልቅ መስቀል በአንገታቸው ላይ ይታይ ነበር፤ መስቀል የእምነት መገለጫ ይሆናል፤ አያጠራጥርም፤ ግን መስቀል ጌጥም ይሆናል! ...”
Subscribe to:
Posts (Atom)