Wednesday, June 25, 2014

እግር ወዶ

አይኔ:-
   አይኗን ጥርሷን ከናፈሯን፣
   ጡት ወገቧን ዳሌ ሽንጧን፣
   አድንቆላት ጎምዥቶላት፣
   ቁልቁል ወረደ፣
   ቁልቁል ነጎደ፣
   እግሯ ሲደርስ ፈዞ ቀረ፣
   ለመመልስ ተቸገረ፣
  አቤት ባቷ ተረከዟ
   አቤት ውበት የጣቶቿ፣
    ሲል ሲለፍፍ ሲመሰክር፣
    ስለ ውበታቸው ሲዘምር፣
    ሄዷል ለካ ብዙ ርቆ፣
    ላልጠፋ አካል እግር ወዶ።
  --------------------------------------
  ተፃፈ ላንቺ (G) 2002 ዓ.ም     
         ©እኔ ነኝ


Saturday, June 21, 2014

እድለቢስቷ

ለስለስ ያለ ንፋስ
           ሽው ሽው ሽውሽውሽው፣
አዋጅ መዓዛዋን ሲያዋህደው፣
የንብ መንጋ
          ዠበብ ዠበብ ዠበበብ ፣
እርፍ ቅስም
          ቅስም ቅስም ቅስምስምስም፣
ማር ስርት የሚጥም፣
ውብ ቢራቢሮዎች
           ብርር ብርር ብርርር፣
ማራኪ ህብር ፍጥር፣
ሲያደርጉ ማየት ነበረ ምኞቷ፣
ያልፈካችው ለጋ እምቡጢቷ፣
  ግና ግና
      በለስላሳው ፋንታ አውሎ ንፋስ፣
     ንቦቹን በዝንብ ጭርንቁስቁስ፣
     ቢራቢሮዎቹን በትንኝ ግብስብስ፣
     ተፈጥሮ ተካችና፣
የምቡጢቷ፣ 
   መዓዛዋ ገማና፣
   ውበቷ ቆሸሸና፣
   ምኞቷ መከነና፣
   ቅረች መና፣ 
   ያልተመረቀላት ፍካቷ፣
   እድለቢስቷ!
==================
     ©እኔ ነኝ
  

Saturday, May 31, 2014

የኋልዮሽ ጉዞ

                                                                                                                                         

መጋቢት  ወር  ነው።  የፋክት  መፅሔትን  ቅፅ  2  ቁጥር  37  እያነበብኩ።  ፕሮፌሰሩ  (/  መስፍን /ማሪያም)  “መጠላለፍ  ወደየት  እየመራን  ነው?”  በሚል  መጠይቅ  የፃፉት  ፅሁፍ  እንደኔ የሃይማኖንቶችን  መቻቻል፣  መፈቃቀር፣  መረዳዳትና  መከባበርን  ልምዱ  አድርጎ  ላደገ ኢትዮጵያዊ ያስደነግጣል፤ ያስፈራል። ፕሮፌሰሩ በፅሁፋቸው ካነሷቸው ሃሳቦች ካንዱ በስተቀር ሌሎቹን የተለያየ ቦታ  ስላነበብኳችው  ቢያስፈሩኝም  አዲሴ  አልነበሩም።  እንደሚከተለው  የገለፁት  ግን  ለኔ  አዲሴና በጣምም ውስጤን የነካኝ ነበር።
“…  አሁን ደግሞ  ሌላ ማዘዣ  ሰማሁ፤  የስ  የሚለው  የውሃ  ጠርሙስ  ላይ  እንስራ  የተሸከመችው ኮረዳ  መስቀል  አድርጋ  ነበር፤  ልጅቱ  ከነ  መስቀሏ  የምትታይበትን  ውሃ  እስላሞች  አንገዛም ስላሉ  ነጋዴዎች  መስቀሉን  አወለቁባትይህንን  ማዘዣ  ላወጣው  አክራሪ  እስላም  ወረባቦ ቅዳሜ ገበያ ሄዶ እንዲጎበኝ አሳስበዋለው፤ ዛሬ ተለውጦ እንደሆነ አላውቅም እንጂ እኔ ብዙ ግዜ ተመላልሼ እንዳየሁት የወረባቦ ኮረዶች ሁሉ ትልልቅ መስቀል በአንገታቸው ላይ ይታይ ነበር፤ መስቀል የእምነት መገለጫ ይሆናል፤ አያጠራጥርም፤ ግን መስቀል ጌጥም ይሆናል! ...”