አይኔ:-
አይኗን ጥርሷን ከናፈሯን፣
ጡት ወገቧን ዳሌ ሽንጧን፣
አድንቆላት ጎምዥቶላት፣
ቁልቁል ወረደ፣
ቁልቁል ነጎደ፣
እግሯ ሲደርስ ፈዞ ቀረ፣
ለመመልስ ተቸገረ፣
አቤት ባቷ ተረከዟ
አቤት ውበት የጣቶቿ፣
ሲል ሲለፍፍ ሲመሰክር፣
ስለ ውበታቸው ሲዘምር፣
ሄዷል ለካ ብዙ ርቆ፣
ላልጠፋ አካል እግር ወዶ።
--------------------------------------
ተፃፈ ላንቺ (G) 2002 ዓ.ም
©እኔ ነኝ
No comments:
Post a Comment