Wednesday, June 25, 2014

እግር ወዶ

አይኔ:-
   አይኗን ጥርሷን ከናፈሯን፣
   ጡት ወገቧን ዳሌ ሽንጧን፣
   አድንቆላት ጎምዥቶላት፣
   ቁልቁል ወረደ፣
   ቁልቁል ነጎደ፣
   እግሯ ሲደርስ ፈዞ ቀረ፣
   ለመመልስ ተቸገረ፣
  አቤት ባቷ ተረከዟ
   አቤት ውበት የጣቶቿ፣
    ሲል ሲለፍፍ ሲመሰክር፣
    ስለ ውበታቸው ሲዘምር፣
    ሄዷል ለካ ብዙ ርቆ፣
    ላልጠፋ አካል እግር ወዶ።
  --------------------------------------
  ተፃፈ ላንቺ (G) 2002 ዓ.ም     
         ©እኔ ነኝ


No comments:

Post a Comment