Saturday, May 31, 2014

የኋልዮሽ ጉዞ

                                                                                                                                         

መጋቢት  ወር  ነው።  የፋክት  መፅሔትን  ቅፅ  2  ቁጥር  37  እያነበብኩ።  ፕሮፌሰሩ  (/  መስፍን /ማሪያም)  “መጠላለፍ  ወደየት  እየመራን  ነው?”  በሚል  መጠይቅ  የፃፉት  ፅሁፍ  እንደኔ የሃይማኖንቶችን  መቻቻል፣  መፈቃቀር፣  መረዳዳትና  መከባበርን  ልምዱ  አድርጎ  ላደገ ኢትዮጵያዊ ያስደነግጣል፤ ያስፈራል። ፕሮፌሰሩ በፅሁፋቸው ካነሷቸው ሃሳቦች ካንዱ በስተቀር ሌሎቹን የተለያየ ቦታ  ስላነበብኳችው  ቢያስፈሩኝም  አዲሴ  አልነበሩም።  እንደሚከተለው  የገለፁት  ግን  ለኔ  አዲሴና በጣምም ውስጤን የነካኝ ነበር።
“…  አሁን ደግሞ  ሌላ ማዘዣ  ሰማሁ፤  የስ  የሚለው  የውሃ  ጠርሙስ  ላይ  እንስራ  የተሸከመችው ኮረዳ  መስቀል  አድርጋ  ነበር፤  ልጅቱ  ከነ  መስቀሏ  የምትታይበትን  ውሃ  እስላሞች  አንገዛም ስላሉ  ነጋዴዎች  መስቀሉን  አወለቁባትይህንን  ማዘዣ  ላወጣው  አክራሪ  እስላም  ወረባቦ ቅዳሜ ገበያ ሄዶ እንዲጎበኝ አሳስበዋለው፤ ዛሬ ተለውጦ እንደሆነ አላውቅም እንጂ እኔ ብዙ ግዜ ተመላልሼ እንዳየሁት የወረባቦ ኮረዶች ሁሉ ትልልቅ መስቀል በአንገታቸው ላይ ይታይ ነበር፤ መስቀል የእምነት መገለጫ ይሆናል፤ አያጠራጥርም፤ ግን መስቀል ጌጥም ይሆናል! ...”